ዳሸን ባንክ ለንግድ ሥራ ለሚጓዙ ደንበኞቹ የዴቢት ካርድ ይፋ አደረገ | Ethiopian Reporter Tenders | 2merkato | ጨረታ

ዳሸን ባንክ ለንግድ ሥራ ለሚጓዙ ደንበኞቹ የዴቢት ካርድ ይፋ አደረገ

ዳሸን ባንክ ከኢትዮጵያ ውጭ ለንግድ ሥራ የሚጓዙ ደንበኞቹ ግብይታቸውን በውጭ ምንዛሪ ለመፈጸም የሚያስችላቸው የዴቢት ካርድ ይፋ ሲያደርግ፣ አቢሲኒያ ባንክ ደግሞ ዓይነ ሥውራን የሚገለገሉበት ኤቲኤም አገልግሎት ላይ አዋለ፡፡ ሁለቱ ባንኮች ሐሙስ ጥቅምት 25 ቀን 2014 ዓ.ም. ይፋ ያደረጉዋቸው አዲሶቹ አገልግሎቶቻቸው በባንክ ኢንዱስትሪው ውስጥ ለመጀመርያ ጊዜ የሚተገበሩ ስለመሆናቸው ባንኮቹ በሰጡዋቸው መግለጫዎች አመልክተዋል፡፡ ዳሸን ባንክ አሜሪካን ኤክስፕሬስ የተሰኘውን …

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በደረቅ ጭነት ላይ ዋጋ ጨመረ | Ethiopian Reporter Tenders | 2merkato | ጨረታ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በደረቅ ጭነት ላይ ዋጋ ጨመረ

በነዳጅ ምርት ላይ የሚጣለው ታክስ እየጨመረ በመምጣቱ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በደረቅ ጭነት የአገልግሎት ዋጋ ላይ የተወሰነ ጭማሪ ማድረጉንና በሌሎች አገልግሎቶቹም ላይ ተመሳሳይ ጭማሪ እንዳደረገ አስታወቀ፡፡ ይህንን አዲሱን ታሪፍም ከሰኞ ጥቅምት 22 ቀን 2014 ዓ.ም. ጀምሮ እንደሚተገበር በተለይ ለደረቅ ጭነት አገልግሎት ተጠቃሚዎቹ በላከው መልዕክት አስታውቋል፡፡ አየር መንገዱ በጭነት አገልግሎቱ ዋጋ ላይ ጭማሪ ማድረጉን ለአገልግሎቱ ተጠቃሚ ደንበኞቹ …

አርች ኮልድ ሶልሽንስ ከ2.9 ቢሊዮን ብር በላይ የሆነ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክት በኢትዮጵያ ለመተግበር ፍላጎት ማሳየቱ ተጠቆመ | Ethiopian Reporter Tenders | 2merkato | ጨረታ

አርች ኮልድ ሶልሽንስ ከ2.9 ቢሊዮን ብር በላይ የሆነ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክት በኢትዮጵያ ለመተግበር ፍላጎት ማሳየቱ ተጠቆመ

መሠረቱን በእንግሊዝ አገር ያደረገና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ድርጅቶች ድጋፍ የሚንቀሳቀስ አርች ኮልድ ሶልሽንስ የተባለ ድርጀት ከ2.9 ቢሊዮን ብር በላይ የሆነ የማቀዝቀዣ መጋዘን ግንባታ ኢንቨስትመንት ፕሮጀክት በኢትዮጵያ ለመተግበር ፍላጎት ማሳየቱ ተጠቆመ፡፡ ድርጅቱ በቂሊንጦ የኢንዱስትሪ ፓርክ የማቀዝቀዣ መጋዘን (የኮልድ ቼይን ፋሲሊቲ) የሚያቀርብ እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን፣ ይህም መድኃኒት፣ ምግብና ሌሎች ሊበላሹ የሚችሉ ምርቶችን በዝቅተኛ የአየር ሁኔታ እንዳይበላሽ ለማቆየት …

ምርት ገበያ ከነባር አባላት በተጨማሪ ሰላሣ አዳዲስ ወንበሮችን ሊሸጥ ነው | Ethiopian Reporter Tenders | 2merkato | ጨረታ

ምርት ገበያ ከነባር አባላት በተጨማሪ ሰላሣ አዳዲስ ወንበሮችን ሊሸጥ ነው

ጨረታው የፊታችን ዓርብ እንደሚከፈት ተጠቁሟል የኢትዮጵያ ምርት ገበያ (ECX) ወንበር ይሸጥ የነበረው ነባር አባላት፣ አባልነታቸውን ትተው ሲወጡ የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ግን 30 አዳዲስ የአባልነት ወንበሮችን ለመሸጥ ጨረታ ማውጣቱ ታወቀ፡፡ ቀደም ብሎ ለአንድ ወንበር እስከ ሰባት ሚሊዮን ብር ድረስ ዋጋ ይሰጥ ስለነበር፣ የፊታችን ዓርብ ጥቅምት 19 ቀን 2014 ዓ.ም. በሚከፈተው ጨረታ ላይ  ከፍተኛ ዋጋዎች እንደሚቀርቡ …

ጎህ ባንክ በመጀመርያ የሥራ ዓመቱ አንድ ቢሊዮን ብር ብድር ሊያቀርብ ነው | Ethiopian Reporter Tenders | 2merkato | ጨረታ

ጎህ ባንክ በመጀመርያ የሥራ ዓመቱ አንድ ቢሊዮን ብር ብድር ሊያቀርብ ነው

በቤት ግንባታና ግዥን ፋይናንስ ለማድረግ የተቋቋመው ጎህ ቤቶች ባንክ በመካከለኛና ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ላሉ ዜጎች የመኖሪያ ቤት አቅርቦትን ለማሻሻል እንደሚሠራና በመጀመርያው ዓመት አንድ ቢሊዮን ብር ብድር እንደሚያቀርብ አስታወቀ፡፡ የመጀመርያው የግል ሞርጌጅ ባንክ የሆነው ጎህ ቤቶች ባንክ የመጀመርያውን ቅርንጫፉን በመክፈት ወደ ሥራም ገብቷል፡፡ የጎህ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ ሙሉጌታ አስማረ እንደገለጹት፣ በተለይ በመካከለኛና ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ …

የአዲስ አበባ ከተማ ገቢዎች ቢሮ በሩብ ዓመት ከ12 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ሰበሰብኩ አለ | Ethiopian Reporter Tenders | 2merkato | ጨረታ

የአዲስ አበባ ከተማ ገቢዎች ቢሮ በሩብ ዓመት ከ12 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ሰበሰብኩ አለ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በተያዘው የበጀት ዓመት የመጀመርያው ሦስት ወራት፣ ከ12.2 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን አስታወቀ፡፡ ቢሮው እስከ ጥቅምት 30 ቀን 2014 ዓ.ም. ድረስ የሚዘልቅ ግብር የማሳወቅና የመሰብሰብ ሥራ እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጾ፣ እስከ መስከረም 2014 ዓ.ም. መጨረሻ ሳምንት ባለው ጊዜ ከግብር አሰባሰቡ የተገኘው ገቢ ከታቀደው በላይ እንደሆነ አስታወቋል፡፡ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ …

Government lifts tax on food items | Ethiopian Reporter Tenders | 2merkato | ጨረታ

Government lifts tax on food items

In an effort to curb and control the rising inflation and enhance the purchasing capacity of the public, the government removed the tax levied on basic commodities such as wheat, edible oil, sugar and rice as of September 3, 2021.   The Value Added Tax (VAT) that has been levied on items such as pasta, …

ዳሸን ባንክ ዳያስፖራው የውጭ ገንዘብ የሚልክበትን ሥርዓት ዘረጋ | Ethiopian Reporter Tenders | 2merkato | ጨረታ

ዳሸን ባንክ ዳያስፖራው የውጭ ገንዘብ የሚልክበትን ሥርዓት ዘረጋ

በሕጋዊ መንገድ ወደ ኢትዮጵያ የሚላከው የውጭ ምንዛሪ ሬሚታንስ በዓመት ወደ አምስት ቢሊዮን ዶላር እንደሚሆን ይገመታል፡፡ ከዳያስፖራው ወደ አገር ቤት በሕጋዊ መንገድ ከሚላከው ምንዛሪ ይልቅ ሕጋዊ ባልሆነ መንገድ የሚላከው የገንዘብ መጠን ብልጫ አለው ተብሎም ይታመናል፡፡ ወደ አገር ውስጥ የሚላከው ገንዘብ ሕጋዊ መስመርን ተከትሎ በባንክ በኩል ላለመላኩ አንዱ ምክንያት፣ በዓለም አቀፍ የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች በኩል ሲላክ የሚጠየቀው …

የውጭ ምንዛሪን በገበያ ዋጋ የተመሠረተ የማድረግ ሒደት | Ethiopian Reporter Tenders | 2merkato | ጨረታ

የውጭ ምንዛሪን በገበያ ዋጋ የተመሠረተ የማድረግ ሒደት

የውጭ ምንዛሪ እጥረትና ከዚሁ ጋር ተያይዘው ያሉ ለዘመናት ያልተፈቱ ችግሮች ዛሬም በኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ ኢኮኖሚያዊ ስንክሳሮች መካከል  ይጠቀሳሉ፡፡ የውጭ ምንዛሪ እጥረቱ ብቻ ሳይሆን የሚገኘውን የውጭ ምንዛሪ ከማስተዳደር አንፃር ያለው ክፍተትም የችግሩ አካል ነው፡፡ ጥቁር ገበያ ጎልቶ መውጣትና ከመደበኛው የምንዛሪ ዋጋ አሻቅቦ መገኘቱ እንዲሁም የጥቁር ገበያው ጉልበት መታየት ሁኔታውን አብሶታል፡፡ ያለውን እጥረት ተከትሎ የሚታየው ሕገወጥ ሥራም …

መርካቶዎች እየተፈተኑባቸው ያሉ ችግሮች | Ethiopian Reporter Tenders | 2merkato | ጨረታ

መርካቶዎች እየተፈተኑባቸው ያሉ ችግሮች

ከሁለት አሠርት በላይ በንግድ ላይ ለተሰማራው አቶ ቴድሮስ ፍቅሩ፣ መርካቶ ማለት ከሰፈርም ከመነገጃነትም በላይ ነው። ‹‹ተወልጄ አድጌ ሀብት ያፈራሁባት ልዩ ሥፍራ ናት›› በማለት መርካቶን ያወድሳል የ43 ዓመቱ ጎልማሳ አቶ ቴድሮስ። በልብስ ምርቶች ንግድ፣ በቤትና ቢሮ ዕቃዎች ማምረትና መሸጥ ላይ የተሰማራው አቶ ቴድሮስ፣ በመርካቶ ሕይወቱን ከልጅነት እስከ አዋቂነት ቢያሳልፍም በመዲናዋ ነግዶ ሀብት ማፍራት ቀላል እንዳልሆነ ያነሳል። ‹‹ምንም እንኳን መርካቶ ለመላው ኢትዮጵያውያን ምርት የሚከፋፈልባትና የሚቀርብባት የሁላችንም የገበያ መዲና ብትሆንም፣ ከቀን ወደ ቀን ሠርቶ መለወጥ እየከበደ ነው›› የሚለው አቶ ቴድሮስ፣ ለዚህም መንግሥትና ሕገወጥ ነጋዴዎችን ይወቅሳል። ከ30 ሺሕ በላይ ሱቆችና ከ700 ሺሕ በላይ ሸማቾች፣ ነጋዴዎችና የንግድ ሠራተኞች በየቀኑ ገብተው ይወጡባታል ተብሎ በምትታመነው መርካቶ፣ የተለያዩ ችግሮችን መመልከት አዲስ ነገር አይደለም። ከሌባና ቀማኞች ገንዘብና ንብረታቸውን ለመጠበቅ ከሚሞክሩ ሸማቾች እስከ በሙስና የተዘፈቁ አንዳንድ የገቢዎች ሠራተኞች ለመሰወር የሚሞክሩ ሠራተኞችን ማየት የተለመደ ጉዳይ ነው። ሁሉም ዓይነት ነጋዴዎች በየፊናቸው እንደ ዘርፋቸው ሁኔታ የተለያዩ ተግዳሮቶች ቢገጥማቸውም ሪፖርተር በመርካቶ በመገኘት ባደረገው ዳሰሳ በአብዛኛው የሚያነሱት ቅሬታዎች ፍትሐዊ የንግድ ሥርዓት አለመኖር፣ ለሙስና በር የከፈተ የተጨማሪ እሴት ታክስ አተገባበርንና የመሠረተ ልማቶች አለሟሟላትን ነው። ‹‹የፍትሐዊንግድያለ›› የፌዴራልም ሆነ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እንዲሁም የወረዳ ንግድ ቢሮዎች የተገልጋዮች ቻርተር ላይ በጉልህ ከተቀመጡ ጉዳዮች አንዱ ፍትሐዊ፣ ግልፅና በውድድር ላይ የተመሠረተ የንግድ ሥርዓትን ማስፈን ነው። ይህንንም መተግበር ከመንግሥት አጀንዳዎች መካከል መሆኑን የመንግሥት ባለሥልጣናት በተደጋጋሚ ያነሳሉ። ይሁን እንጂ የተጻፈው አልያም የተወራው ከትግበራው አኳያ ፈፅሞ የተለየ መሆኑን ነጋዴዎች ይናገራሉ። በመርካቶ አመዴ ተራ በጫማ ችርቻሮ ንግድ ላይ የተሰማሩት አቶ አማኑኤል መንግሥቱ እንደሚናገሩት፣ የንግድ ሥርዓቱ ላይ የፍትሐዊነት ችግሮች መታየት ከጀመሩ ሰንበትበት ብለዋል። የመንገድ ላይ ንግድ መስፋፋትን እንደ ማሳያ የሚያነሱት አቶ …