ሕብረት ባንክ አ/ማ በሞጆ ቅርንጫፍ በኩል ለሰጠው ብድር በመያዣነት የያዘውንና ከዚህ በታች የተመለከተውን የመኖሪያ ቤት በአዋጅ ቁጥር 97/90 እና 216/92 በተሰጠው ስልጣን መሰረት በግልጽ ሐራጅ (ጨረታ) አወዳድሮ ይሸጣል፡፡

hibret-bank-done-logo-reportertenders-6

Overview

  • Category : House & Building Foreclosure
  • Posted Date : 01/30/2023
  • Closing Date : 02/27/2023
  • Phone Number : 0115573772
  • Source : Reporter

Description

ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ የሐራጅ ማስታወቂያ፤

ሕብረት ባንክ አ/ማ በሞጆ ቅርንጫፍ በኩል ለሰጠው ብድር በመያዣነት የያዘውንና ከዚህ በታች የተመለከተውን የመኖሪያ ቤት በአዋጅ ቁጥር 97/90 እና 216/92 በተሰጠው ስልጣን መሰረት በግልጽ ሐራጅ (ጨረታ) አወዳድሮ ይሸጣል፡፡

የቅርንጫፍ ስምየተበዳሪ ስምየአስያዥ ስምቤቱ የሚገኝበት አድራሻና የቦታው ስፋትየካርታ ቁጥርየሐራጅ መነሻ ዋጋ በብርሐራጁ የሚካሄድበት ቀንና ሰዓት
 

ሞጆ

 

አቶ ፀጉ አለማየሁ

አቶ አለማየሁ አንዳርሳሞጆ ከተማ፣ቀበሌ 01፣የቦታ ስፋት 450 ካ/ሜ፣ለመኖሪያ አገልግሎት የሚውል ቤት2689/242/A1-Aa/98 

1,452,935.00

የካቲት 21 ቀን 2015 ዓ.ም ከጠዋቱ ከ4፡00    እስከ 6፡00 ሰዓት

የሐራጅ ደንቦች

  1. ተጫራቾች የሐራጁን መነሻ ዋጋ አንድ አራተኛ በሕብረት ባንክ አ/ማ (Hibret Bank S.C) ስም የተዘጋጀ የባንክ ክፍያ ማዘዣ (ሲ.ፒ.ኦ.) ብቻ በማስያዝ መጫረት ይችላሉ፡፡
  2. አሸናፊ የሆነው ተጫራች ያሸነፈበትን ቀሪ ገንዘብ በአስራ አምስት ቀናት ዉስጥ አጠቃልሎ ካልከፈለ ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ሆኖ ሐራጁ ይሰረዛል፡፡ በተጨማሪም ንብረቱ ድጋሚ ለሐራጅ ሲቀርብ ለሚታየው የዋጋ ልዩነት ይጠየቃል፡፡
  3. በሐራጅ ላይ መገኘት የሚችሉት ተጫራቾች፣ተበዳሪዎች እና አስያዦች ብቻ ናቸው፡፡
  4. ተጫራቾች በሐራጅ ለመሳተፍ ሲመጡ መታወቂያ መያዝ ይገባቸዋል፡፡ተጫራቾች የሕግ ሰውነት የተሰጣቸው አካላት ከሆኑ ሕጋዊ ሰውነት ያገኙበትን የዋና ምዝገባ ምስክር ወረቀት እንዲሁም ሐራጁን ለመሳተፍ የቀረበው ሰው ስልጣኑን የሚያሳይ በሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ጽ/ቤት ወይም በሌላ ተመሳሳይ ፅ/ቤት የፀደቀ የመመሥረቻ ጽሑፍ፣የመተዳደሪያ ደንብ፣ቃለ ጉባኤ ወይም የውክልና ሰነድ ይዞ መቅረብ አለበት፡፡
  5. የሐራጅ ሽያጩ የሚካሄደው የመያዣው ንብረት በሚገኝበት ቦታ ላይ ነው፡፡
  6. የተጫራቾች ምዝገባ ከሐራጁ መዝጊያ ሰዓት ሰላሳ ደቂቃ በፊት ይደረጋል፡፡
  7. ለሐራጅ የቀረበውን ንብረት ለመጎብኘት የሚፈልጉ ተጫራቾች ከሕብረት ባንክ ሕግ አገልግሎት መምሪያ(ከቅርንጫፉ) ጋር አስቀድሞ ቀጠሮ በመያዝ ከጨረታው ቀን ሶስት ቀናት አስቀድሞ መጎብኘት ይችላሉ፡፡
  8. የተጨማሪ እሴት ታክስ እና ሌሎች ገዥ እንዲከፍላቸው በህግ የተወሰኑ የታክስና ግብር የስም ማዛወሪያ እንዲሁም የሊዝ ክፍያዎችን ጭምር ገዥ(የጨረታው አሸናፊ) ይከፍላል፡፡
  9. ባንኩ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  • ለተጨማሪ መረጃ የሕግ አገልግሎት መምሪያ በስልክ ቁጥር 0115-57-37-72 /0114-70-03-15/47/41-03 ወይም ሞጆ ቅርንጫፍ 0221-16-01-62/05-48/01-45 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡