ቡሳ ጎኖፋ ማይክሮፋይናንስ አ.ማ. ያገለገለ መኪና ባለበት ሁኔታ በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡

Buussaa-Gonofaa-Microfinance-logo

Overview

  • Category : Vehicle Sale
  • Posted Date : 05/29/2021
  • Closing Date : 06/14/2021
  • Phone Number : 0114162621
  • Source : Reporter

Description

የጨረታ ማስታወቂያ

ቡሳ ጎኖፋ ማይክሮፋይናንስ አ.ማ. የድርጅቱ ንብረት የሆነውን ስቴሽን ዋገን፣ማሕንድራ የሠለዳ ቁጥሩ ኮድ 3-A23915 አ.አ. ሞዴል ስኮርፒዮ የሆነዉን ያገለገለ መኪና ባለበት ሁኔታ በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡ የጨረታ መነሻ ዋጋ ብር 550,000.00 (አምስት መቶ ሃምሳ ሺህ ብር) ሲሆን፤

  1. የመኪውን ሁኔታ ማየት የሚፈልጉ ተጫራቾች መኪናው ባለበት የድርጅቱ ዋና መ/ቤት ከኢትዮጲያ ንግድ ባንክ ጠመንጃ ያዥ ቅርንጫፍ ፊት ለፊት ከሚኘው ቶታል ማደያ ጀርባ ቤተ ሳይዳ ሕንፃ ቅጥር ግቢ በምድር ቤት የመኪና ማቆሚያ ውስጥ ዘወትር በስራ ሰዓት ጠዋት ከ 3፡00-4፡00 ከሰዓት ከ 10፡00-11፡00 ሰዓት በመገኘት ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ሰኔ 7 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስ ማየት ይችላሉ፡፡
  2. ተጫራቾች ለሽያጭ የቀረበውን መኪና ዋጋ በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ እስከ ሰኔ 7 ቀን 2013 ዓ.ም ከቀኑ  11፡00  ስዓት ድረስ  ከላይ በተጠቀሰው በድርጅቱ ዋና መ/ቤት  ፐርሶኔል ክፍል 4ኛ ፎቅ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  3. ተጫራቾች ለሚጫረቱበት ተሽከርካሪ የመነሻ ዋጋ 10% ( አስር በመቶ) የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ ክፍያ ማዘዣ (C.P.O) ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ ተጫራቹ በጨረታው ከተሸነፈ በማስያዣ ያስያዘው ገንዘብ ወዲያውኑ ተመላሽ ይሆንለታል፡፡
  4. ጨረታው ሰኔ 10 ቀን 2013 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት በዋናው መ/ቤት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸውና ታዛቢዎች በተገኙበት ይከፈታል፡፡
  5. ተጫራቾች በጨረታው ያሸነፉትን ተሽከርካሪ ሙሉ ክፍያ ጨረታውን ካሸነፉበት ቀን ጀምሮ በ 7 ቀናት ውስጥ በመክፈል መኪናውን መረከብ ይኖርባቸዋል፡፡
  6. የጨረታው አሸናፊ ለስም ማዘዋወሪያና ሌሎች ተጓዳኝ ክፍያዎችን በሙሉ የሚሸፍን ይሆናል፡፡
  7. ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0114-16-26-21 በመደወል ወይንም ከላይ በተጠቀሰው የድርጅቱ አድራሻ በግንባር ቀርቦ መጠየቅ ይቻላል፡፡
  8. መስሪያ ቤቱ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡