አቢሲንያ ባንክ /አ.ማ/ ለሰጠው ብድር በዋስትና የያዘውንና በሠንጠረዡ የተመለከተዉን ተሽከርካሪ ከነተሳቢው ሳይነጣጠል በአዋጅ ቁጥር 1147/2011 መሠረት ንብረቱ ባለበት ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
Overview
- Category : Vehicle Foreclosure
- Posted Date : 01/21/2023
- Phone Number : 0115150711
- Source : Reporter
- Closing Date : 02/08/2023
Description
በድጋሚ የወጣ የሐራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ
አቢሲንያ ባንክ /አ.ማ/ ለሰጠው ብድር በዋስትና የያዘውንና በሠንጠረዡ የተመለከተዉን ተሽከርካሪ ከነተሳቢው ሳይነጣጠል በአዋጅ ቁጥር 1147/2011 መሠረት ንብረቱ ባለበት ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም ተጫራቾች ለጨረታ ከመቅረባቸው በፊት የሚከተሉትን ደንቦች መገንዘብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ንብረት የጨረታ መነሻ ዋጋውን ¼ (አንድ አራተኛ) በባንክ በተረጋገጠ ቼክ ወይም ሲ.ፒ.ኦ በአቢሲንያ ባንክ (አ.ማ) ስም በማሰራት ለጨረታ ማስከበሪያ በማስያዝ በጨረታው ላይ መሳተፍ ይችላል፡፡
- የጨረታው አሸናፊ አሸናፊነቱ ከባንኩ በደብዳቤ ከተገለጸለት ቀን ጀምሮ ያሸነፈበትን ጠቅላላ ዋጋ በ15 (አስራ አምስት) ቀናት ውስጥ አጠቃሎ ከፍሎ በጨረታ ያሸነፈበትን ንብረት/ንብረቶች መረከብ ይኖርበታል፡፡ በእነዚህ ቀናት ውስጥ ካልከፈለ ጨረታው ተሰርዞ ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ይሆናል፡፡ በጨረታው ለተሸነፉት ተጫራቾች ያስያዙት ሲ.ፒ.ኦ ይመለስላቸዋል፡፡
- ተበዳሪው/መያዣ ሰጪው በሐራጁ ቀንና ሰዓት በቦታው መገኘት ይችላሉ፡፡
- የጨረታው አሸናፊ ከሚገዛው ንብረት ጋር የተያያዙ ማናቸውም ለመንግስት የሚከፈሉ ክፍያዎችን ፣ ግብር ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ 15% እንዲሁም ከስም ዝውውር ጋር የሚገናኙ ማናቸውም ወጪዎች ገዢ ይከፍላል፡፡
- ንብረቱን በሥራ ሰዓት ፕሮግራም አሲዞ ለመጎብኘት ወይም ለማየት ይቻላል፡፡
- የጨረታው ቦታ አዲስ አበባ ከተማ፣ ቂርቆስ ክ/ከተማ፣ ወረዳ 4፣ የህብረት ባንክ አ.ማ ዋና መስርያ ቤት የነበረው ህንፃ ጎን ካለው አልፓውሎ ህንፃ 3ኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው የባንኩ ሕግ መምሪያ ነው፡፡
- ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0115-150711 እና 0115 54 67 37/36 በመደወል መጠየቅ ይቻላል፡፡
- ባንኩ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ተ.ቁ | የተበዳሪው ስም | ከተበዳሪዉ የሚፈለግበት ቀሪ ዕዳ | የመያዣ ሰጪዉ ስም | የተሸከርካሪዉ ዓይነትና የተሰራበት ዘመን | የሰሌዳ ቁጥር
|
የሻንሲ ቁጥር | የሞተር ቁጥር | የጨረታ መነሻ ዋጋ ብር | ጨረታዉ የሚካሄድበት
ቀን |
የምዝገባ ሰዓት | የጨረታ ሰዓት
|
ንብረቱ ያለበት ሁኔታ | |
1 |
አቶ አለማየሁ ማሞ |
እስከ ጥር7 ቀን 2012 ዓ.ምብር 23,214,865 |
አቶ አለማየሁ ማሞ |
ኢቪኮ ፈሳሽ ጭነት |
ኢት-03-65541 |
WJME3TRE1EC285565 |
F3BEE681G*B220-221890 |
5,973,274.50 |
30/05/2015 ዓ.ም |
4፡305፡30 |
5፡30-6፡00 |
ካምቢዮ የተበላሽ |
|
መስፍን ፈሳሽ ጭነት ተሳቢ | ኢት-03-19865 | TT0988-14 | – |