አቢሲንያ ባንክ /አ.ማ/ ለሰጠው ብድር በዋስትና የያዘውንና በሠንጠረዡ የተመለከቱትን ንብረቶች በአዋጅ ቁጥር 97/90 (እንደተሻሻለው) መሠረት ንብረቶቹ ባሉበት ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡

Overview

  • Category : House & Building Foreclosure
  • Posted Date : 06/05/2021
  • Closing Date : 07/22/2021
  • Phone Number : 0115150711
  • Source : Reporter

Description

የሐራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ

አቢሲንያ ባንክ /አ.ማ/ ለሰጠው ብድር በዋስትና የያዘውንና በሠንጠረዡ የተመለከቱትን ንብረቶች በአዋጅ ቁጥር 97/90 (እንደተሻሻለው) መሠረት ንብረቶቹ ባሉበት ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም ተጫራቾች ለጨረታ ከመቅረባቸው በፊት የሚከተሉትን ደንቦች መገንዘብ ይኖርባቸዋል፡፡

  • ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ንብረት የጨረታ መነሻ ዋጋውን ¼ (አንድ አራተኛ) በባንክ በተረጋገጠ ቼክ ወይም ሲ.ፒ.ኦ በአቢሲንያ ባንክ (አ.ማ) ስም በማሰራት ለጨረታ ማስከበሪያ በማስያዝ በጨረታው ለመሳተፍ ይችላሉ፡፡
  • የጨረታው አሸናፊ አሸናፊነቱ ከባንኩ በደብዳቤ ከተገለጸለት ቀን ጀምሮ ያሸነፈበትን ጠቅላላ ዋጋ በ15 (አስራ አምስት) ቀናት ውስጥ አጠቃሎ ከፍሎ በጨረታ ያሸነፈበትን ንብረት/ንብረቶች መረከብ ይኖርበታል፡፡ በእነዚህ ቀናት ውስጥ ካልከፈለ ጨረታው ተሰርዞ ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ይሆናል፡፡ በጨረታው ለተሸነፉት ተጫራቾች ያስያዙት ሲ.ፒ.ኦ ይመለስላቸዋል፡፡
  • ተበዳሪው/መያዣ ሰጪው በሐራጁ ቀንና ሰዓት በቦታው መገኘት ይችላሉ፡፡ ነገር ግን ባይገኙ ሐራጁ በሌሉበት ይካሄዳል፡፡
  • የጨረታው አሸናፊ ከሚገዛው ንብረት ጋር የተያያዙ ማናቸውም ለመንግስት የሚከፈሉ ክፍያዎችን ፣ ግብር ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ 15% እንዲሁም ከስም ዝውውር ጋር የሚገናኙ ማናቸውም ወጪዎችንም ገዢ ይከፍላል፡፡ ውዝፍ የሊዝ ክፍያ ካለ ባንኩ የሚከፍል ሲሆን ቀሪ የሊዝ ክፍያ ገዢ ከሚመለከተው የመንግስት አካል ጋር ይዋዋላል፡፡
  • ንብረቶቹን በሥራ ሰዓት ፕሮግራም አሲዞ ለመጎብኘት ወይም ለማየት ይቻላል፡፡
  • በባንኩ ብድር ፖሊሲ እና መመሪያ መሠረት መስፈርቱን ለሚያሟሉ የጨረታው ከፍተኛ ዋጋ አቅራቢዎች ባንኩ ከፊል ብድር ሊሰጥ ይችላል፡፡
  • የጨረታው ቦታ አዲስ አበባ ከተማ ቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 4 ህብረት ባንክ አ.ማ ዋና መስሪያ ቤት ጎን ካለው አልፓውሎ ህንጻ 3ኛ ፎቅ በባንኩ ህግ መምሪያ ነው፡፡
  • ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0115-150711 እና 0115 54 67 37/36 አ.አ በመደወል መጠየቅ ይቻላል፡፡
  • ባንኩ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

 

t.q$

ከተበዳሪው የሚፈለግበት

ቀሪ ዕዳ

 

የመያዣ

ስጪው ስም

የንብረቱ ዓይነትና አገልግሎት

የቦታው ስፋት

የባለቤትነት ማረጋገጫ ካርታ ቁጥር

ንብረቱ የሚገኝበት አድራሻ

የጨረታ

መነሻ ዋጋ

በብር

ጨረታው የሚካሄድበት ቀን

 

የምዝገባ

ሰዓት

የጨረታ

ሰዓት

 

ጨረታው የወጣበት ጊዜ

 

 

1

እስከ ጥር 20 ቀን 2012 ብር 4,328,154.23

ተበዳሪው

በግንባታ ላይ ያለ G+2+T   መኖሪያ ቤት

 230

 ካ.ሜ

ቦሌ/ሊዝ/ጨ4/43/ 11/14/10654/00

በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክ/ከ ወረዳ 10

7,019,400.00

 

ሐምሌ 6 ቀን 2013ዓ.ም

 4:30-5:30

 5፡30-6፡00

 

በድጋሚ

 

 

2

እስከ ጥር 04 ቀን 2013 ዓ.ም ብር 7,638,182.27

ተበዳሪው

G+2 እና  G+1 መኖሪያ ቤት

300 ካ.ሜ

AA000090602133

አ.አ ኮ/ቀራንዮ ክ/ከተማ፣ወረዳ 06

8,180,860.78

ሐምሌ 8 ቀን 2013ዓ.ም

 4:30-5:30

5:30-6:00

 

ለመጀመሪያ ጊዜ

 

3

እስከ ታህሳስ  03

 ቀን 2012 ዓ.ም    ብር 4,335,283.01

ተበዳሪው

መጋዘን

500          ካ.ሜ

370/3101/97

በኦ/ብ/ክ/መንግስት ሰንዳፋ፣ከተማ      ቀበሌ 01

1,855,000.00

ሰኔ 30 ቀን

 2013 ዓ.ም

4፡30-5፡30

5፡30-6፡00

 

ለመጀመሪያ ጊዜ

 

 

4

እስከ እ.ኤ.አ እስከ 13/03/2019 ድረሰ

 ብር 2,125,393.47

ተበዳሪው

G+2     መኖሪያ ቤት

250

ካ.ሜ

ግ/20/4/1159/2003

ባህር ዳር

ቀበሌ 14

3,811,710.00

ሐምሌ 15 ቀን 2013 ዓ.ም

4፡30-5፡30

5፡30-6፡00

 

ለሁለተኛ ጊዜ