አቢሲንያ ባንክ /አ.ማ/ በዋስትና የያዘውን ንብረት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል

Abissiniya-Bank

Overview

  • Category : House & Building Foreclosure
  • Posted Date : 08/01/2021
  • Closing Date : 08/16/2021
  • Phone Number : 0115150711
  • Source : Reporter

Description

የሐራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ

አቢሲንያ ባንክ /አ.ማ/ ለሰጠው ብድር በዋስትና የያዘውንና በሠንጠረዡ የተመለከተውን ንብረት በአዋጅ ቁጥር 97/90 (እንደተሻሻለው) መሠረት ንብረት ባለበት ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም ተጫራቾች ለጨረታ ከመቅረባቸው በፊት የሚከተሉትን ደንቦች መገንዘብ ይኖርባቸዋል፡፡

  • ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ንብረት የጨረታ መነሻ ዋጋውን ¼ (አንድ አራተኛ) በባንክ በተረጋገጠ ቼክ ወይም ሲ.ፒ.ኦ በአቢሲንያ ባንክ (አ.ማ) ስም በማሰራት ለጨረታ ማስከበሪያ በማስያዝ በጨረታው ለመሳተፍ ይችላሉ፡፡
  • የጨረታው አሸናፊ አሸናፊነቱ ከባንኩ በደብዳቤ ከተገለጸለት ቀን ጀምሮ ያሸነፈበትን ጠቅላላ ዋጋ በ15 (አስራ አምስት) ቀናት ውስጥ አጠቃሎ ከፍሎ በጨረታ ያሸነፈበትን ንብረት/ንብረቶች መረከብ ይኖርበታል፡፡ በእነዚህ ቀናት ውስጥ ካልከፈለ ጨረታው ተሰርዞ ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ይሆናል፡፡ በጨረታው ለተሸነፉት ተጫራቾች ያስያዙት ሲ.ፒ.ኦ ይመለስላቸዋል፡፡
  • ተበዳሪው/መያዣ ሰጪው በሐራጁ ቀንና ሰዓት በቦታው መገኘት ይችላሉ፡፡ ነገር ግን ባይገኙ ሐራጁ በሌሉበት ይካሄዳል፡፡
  • የጨረታው አሸናፊ ከሚገዛው ንብረት ጋር የተያያዙ ማናቸውም ለመንግስት የሚከፈሉ ክፍያዎችን፣ 15% ቫት እንዲሁም ከስም ዝውውር ጋር የሚገናኙ ማናቸውም ወጪዎች ገዢ ይከፍላል፡፡ውዝፍ የሊዝ ዕዳ ባንኩ የሚከፍል ሲሆን ቀሪ የሊዝ ክፍያ ዕዳ ወደ አሸናፊው /ገዢ የሚተላለፍ ይሆናል፡፡
  • ንብረቶቹን በሥራ ሰዓት ፕሮግራም አሲዞ ለመጎብኘት ወይም ለማየት ይቻላል፡፡
  • በባንኩ ብድር ፖሊሲ እና መመሪያ መሠረት መስፈርቱን ለሚያሟሉ የጨረታው ከፍተኛ ዋጋ አቅራቢዎች ባንኩ ከፊል ብድር ሊሰጥ ይችላል፡፡
  • የጨረታው ቦታ አ.አ ከተማ ቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 4 ህብረት ባንክ አ.ማ ዋና መስሪያ ቤት ጎን ካለው አልፓውሎ ህንጻ 3ኛ ፎቅ በባንኩ ህግ መምሪያ ነው፡፡
  • ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0115-150711 እና 0115 54 67 37/36 አ.አ በመደወል መጠየቅ ይቻላል፡፡
  • ባንኩ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

 

 

t.q$

የተበዳሪው ስም ከተበዳሪው የሚፈለግበት

ቀሪ ዕዳ

የመያዣው ሰጪው ስምየንብረቱ ዓይነትና አገልግሎትየቦታው ስፋትየባለቤት ማረጋገጫ ካርታ ቁጥር ንብረቱ የሚገኝበት አድራሻየጨረታ መነሻ ዋጋ ጨረታው የሚካሄድበት ቀን  

የምዝገባ

ሰዓት

የጨረታ

ሰዓት

ጨረታው የወጣበት ጊዜ
 

1

አቶ ወንደሰን አንበሉእስከ የካቲት 17  ቀን 2012 ዓ.ም ድረስ     ብር 2,317,410.00ተበዳሪውመኖሪያ ቤት242.00ካ.ሜቦሌ7/12/6/8/1/3805/3214/5739/02ቦሌ ክ/ከተማ

ወረዳ 07

5,889,148.16መስከረም 13 ቀን 2014 ዓ.ም4:30-5:30 5:30-6:00 

ለመጀመሪያ  ጊ ጊዜ

 

2

ሀትና ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበርእስከ ግንቦት 13  ቀን 2013ዓ.ም ድረስ         ብር11,622,275.51ወ/ሮ ሳባ አጽብሃመኖሪያ ቤት250.00ካ.ሜቦሌ9/74/4/5/ነ/301/504/01ቦሌ ክ/ከተማ

ወረዳ 09

8,435,000.00መስከረም 05 ቀን 2014 ዓ.ም4:30-5:30 5:30-6:00 

በድጋሚ

 

3

 

አቶ ሞላ ተመስገን

እስከ ሚያዝያ 13 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስ ብር15,400,000.00ተበዳሪውG+2

መኖሪያ ቤት

127.3ካሜ AA0000907013827አዲስ አበባ ኮልፌ ቀራንዮ

ወረዳ 7

 6,410,193.40ነሐሴ 20  ቀን 2013 ዓ.ም4፡30-5፡30 

 

5፡30-6፡00

 

በድጋሚ