አቢሲንያ ባንክ /አ.ማ/ የሰጠው ብድር ባለመከፈሉ በእዳ ማካካሻት የወረሳቸውን ንብረቶች በአዋጅ ቁጥር 97/90 (እንደተሻሻለው) 216/92 መሠረት ንብረቶቹ ባሉበት ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
Overview
- Category : House & Building Foreclosure
- Phone Number : 0583209660
- Source : Reporter
- Posted Date : 01/28/2023
- Closing Date : 02/26/2023
Description
የሐራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ
አቢሲንያ ባንክ /አ.ማ/ የሰጠው ብድር ባለመከፈሉ በእዳ ማካካሻት የወረሳቸውን ንብረቶች በአዋጅ ቁጥር 97/90 (እንደተሻሻለው) 216/92 መሠረት ንብረቶቹ ባሉበት ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም ተጫራቾች ለጨረታ ከመቅረባቸው በፊት የሚከተሉትን ደንቦች መገንዘብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ንብረት የጨረታ መነሻ ዋጋውን ¼ (አንድ አራተኛ) በባንክ በተረጋገጠ ቼክ ወይም ሲ.ፒ.ኦ በአቢሲንያ ባንክ (አ.ማ) ስም በማሰራት ለጨረታ ማስከበሪያ በማስያዝ በጨረታው ለመሳተፍ ይችላሉ፡፡
- ስለጨረታው አካሄድ እና ንብረቶች ዝርዝር መግለጫ የያዘውን ሰነድ ንብረቶች በሚገኙበት የባንኩ ቅርንጫፎ በመቅረብ የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ) በመክፈል ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ መውሰድ ይቻላል፡፡
- የጨረታው አሸናፊ አሸናፊነቱ ከባንኩ በደብዳቤ ከተገለጸለት ቀን ጀምሮ ያሸነፈበትን ጠቅላላ ዋጋ በ15 (አስራ አምስት) ቀናት ውስጥ አጠቃሎ ከፍሎ በጨረታ ያሸነፈበትን ንብረት/ንብረቶች መረከብ ይኖርበታል፡፡ በእነዚህ ቀናት ውስጥ ካልከፈለ ጨረታው ተሰርዞ ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ይሆናል፡፡ በጨረታው ለተሸነፉት ተጫራቾች ያስያዙት ሲ.ፒ.ኦ ይመለስላቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ንብረቱን ለመግዛት የሚሰጡትን ዋጋ ከጨረታ ሰነዱ ላይ በተያያዘው የዋጋ ማቅረቢያ ቅፁ ካሰፈሩ በኋላ የጨረታ ማስከበሪያና ሌሎች አስፈላጊ መረጃዎችን በማያያዝ በስም በታሸገ ፖስታ ዘወትር በስራ ሰዓት እስከ ጨረታው መካሄጃ ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ድረስ በቅርንጫፎች ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ አስመዝግበው ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በጋዜጣው በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት ይከፈታል፡፡
- የጨረታው አሸናፊ ከሚገዛው ንብረት ጋር የተያያዙ ማናቸውም ለመንግስት የሚከፈሉ ክፍያዎችን ፣ ግብር ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ 15% እንዲሁም ከስም ዝውውር ጋር የሚገናኙ ማናቸውም ወጪዎችንም ገዢ ይከፍላል፡፡ ውዝፍ የሊዝ ክፍያ ካለ ባንኩ የሚከፍል ሲሆን ቀሪ የሊዝ ክፍያ ገዢ ከሚመለከተው የመንግስት አካል ጋር ይዋዋላል፡፡
- ንብረቶቹን በሥራ ሰዓት ፕሮግራም አሲዞ ለመጎብኘት ወይም ለማየት ይቻላል፡፡
- በባንኩ ብድር ፖሊሲ እና መመሪያ መሠረት መስፈርቱን ለሚያሟሉ የጨረታው ከፍተኛ ዋጋ አቅራቢዎች ባንኩ ከፊል ብድር ሊሰጥ ይችላል፡፡
- የጨረታው ቦታ ንብረቶቹ በሚገኙበት ስፍራ ነው፡፡
- ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 058-320-9660 እና 058-320-6761 ባህር ዳር በመደወል መጠየቅ ይቻላል፡፡
- ባንኩ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ተ.ቁ | የተበዳሪው ሙሉ ስም | የመያዣ ስጪው ስም | የንብረቱ ዓይነትና አገልግሎት | የቦታው ስፋት | የባለቤትነት ማረጋገጫ ካርታ ቁጥር | ንብረቱ የሚገኝበት አድራሻ | የጨረታ መነሻ ዋጋ በብር | ጨረታው የወጣበት ጊዜ | ጨረታው የሚካሄድበት ቀን |
1 | ጂ.ዜድ.ኤ ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር | ተበዳሪው | ለኢንዱስትሪ የሚሆን ጅምር መካዘን | 8000 ካ.ሜ | 1307/2009 | አማራ ክልል ሞጣ ከተማ | 11,683,575.00 | ለመጀመሪያ ጊዜ | የካቲት 27 ቀን 2015 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00-6፡00 ሰዓት |
2
| አቶ ዳዊት እሸቱ
| ተበዳሪው | ለመኖሪያ | 150 ካ.ሜ | 11834/10 | ቡሬ ከተማ ቀበሌ 03 | 715,680.00 | ለመጀመሪያ ጊዜ | የካቲት 28 ቀን 2015 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00-6፡00 |
አንተነህ ብርሃኔ | ለመኖሪያ | 150 ካ.ሜ | 11735/10 | ቡሬ ከተማ ቀበሌ 03 | 543,216.00 | ለመጀመሪያ ጊዜ | የካቲት 28 ቀን 2015 ዓ.ም ከሰዓት 8፡00-10፡30 | ||
ፍስሃ ተስፋዬ | መኖሪያ ቤት | 150 ካ.ሜ | 11528/10 | ቡሬ ከተማ ቀበሌ 03 | 411,731.25 | ለመጀመሪያ ጊዜ | የካቲት 29 ቀን 2015 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00-6፡00 | ||
4 | ክንዱ አለበል ሽፈራው | ተበዳሪው | መጋዘን | 500 ካ.ሜ | ክ-262-/2008 | አማራ ክልል ገንደውሃ ከተማ | 10,894,500.00 | ለመጀመሪያ ጊዜ | መጋቢት 01 ቀን 2015 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00-6፡00 |