አዲስ ኢንተርናሽናል ባንክ አ.ማ ለሰጠዉ ብድር በዋስትና የያዘውን ንብረት በአዋጅ ቁጥር 97/1990 በተሰጠዉ ስልጣን መሰረት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
Overview
- Category : House & Building Foreclosure
- Posted Date : 02/06/2023
- Closing Date : 02/28/2023
- Phone Number : 0115571934
- Source : Reporter
Description
ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ የሐራጅ ማስታወቂያ
አዲስ ኢንተርናሽናል ባንክ አ.ማ ለሰጠዉ ብድር በዋስትና የያዘውን ንብረት በአዋጅ ቁጥር 97/1990 በተሰጠዉ ስልጣን መሰረት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡ በዚሁ መሰረት ማንኛዉም ተጫራች ሐራጁ በሚካሄድበት ቀን ጨረታው በሚከናወንበት ቦታ በመገኘት በጨረታዉ ተወዳድሮ ንብረቱን እንዲገዛ ተጋብዟል፡፡
ተ.ቁ | የተበዳሪዉ ስም | የንብረት አስያዥ ስም | አበዳሪውቅርንጫፍ | ለጨረታ የቀረበዉ የመያዣ ንብረት አይነት | ንብረቱ የሚገኝበት አድራሻ | የባለቤትነትማረጋገጫ ቁጥር | የቦታዉ ስፋት በካሬ ሜትር | የጨረታዉመነሻ ዋጋ | ጨረታዉ የሚከናወንበት ቦታ | ጨረታዉ የሚከናወንበት ቀንና ሰዓት | |
ከተማ | ክ/ከተማ እና ወረዳ | ||||||||||
1. | በላይ ወላሻ ሸጎ | በላይ ወላሻ ሸጎ | ሲዳሞ ተራ | የቡና ማቀናበሪያቦታ | ደቡብ ሸካ | ጋማደሮ ከተማ አንድራጫ ወረዳ ቀበሌ 1 | 522/08/2010 | 12.35 ሄክታር | 4,500,350.39 | አዲስ አበባ አዲስ ኢንተርናሽል ባንክ አ.ማ ዋናው መስሪያ ቤት ፤ዝቀላ ኮምፕሌክስ ህንጻ 3ኛ ፎቅ | የካቲት 30 ቀን 2015 ዓ/ም ከሰዓት ከ 8.00- 10.00 ሰዓት |
- ተጫራቾች የጨረታዉን መነሻ ዋጋ 25% በባንኩ የክፍያ ማዘዣ ሰነድ(cpo) አሰርቶ በጨረታዉ ቀን ጨረታው በሚካሄድበት ቦታ በመቅረብ መመዝገብ እና በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ፡፡
- ጨረታዉ በማስታወቂያዉ ላይ በተጠቀሰዉ ቀንና ሰዓት ባለዕዳዎቹ ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸዉ፣ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸዉ፣ታዛቢዎች በተገኙበት፣የመያዣ ንብረቱ በሚገኝበት የሚካሄድ ይሆናል፡፡ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው እንዲሁም አስያዦች ባይገኙም ጨረታው በተባለው ቀንና ሰዓት የሚከናወን ይሆናል፡፡
- የጨረታዉ አሸናፊ ያሸነፈበትን ዋጋ ጨረታዉ ከተከናወነበት ማግስት ጀምሮ በሚቆጠር 15 ቀን ዉስጥ ለባንኩ ገቢ ማድረግ ይኖርበታል፡፡በእነዚህ ቀናት ዉስጥ ካልከፈለ ግን ለጨረታ ያስያዘዉ ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ሆኖ ጨረታዉ ተሰርዞ ለሐራጅ የሚቀርብ ይሆናል፡፡በጨረታዉ ተሳትፈዉ ላላሸነፉት ተጫራቾች ያስያዙት ጥሬ ገንዘብ ወይም ሲፒኦ ወዲያኑ ተመላሽ ይደረግላቸዋል፡፡
- ኃ/የተ/የግል ማህበርን ወይም አክሲዮን ማህበርን ወክሎ መጫረት የሚፈልግ ሥራ አስኪያጅ ወይም ም/ሥራ አስኪያጅ የድርጅት የመመስረቻ ጽሑፍ እና መተዳደሪያ ደንብ ይዞ መቅረብ ያለበት ሲሆን የሥራ አስኪያጅ ወይም የም/ሥራ አስኪያጅ ለዉጥ ተደርጎ ከሆነ ይህንኑ የሚገልጽ በሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ጽ/ቤት ቃለ ጉባኤ ከመመስረቻ ጽሑፍ እና መተዳደሪያ ደንብ ጋር ይዞ መቅረብ አለበት፡፡
- የጨረታዉ አሸናፊ ለመንግስት የሚከፈለዉን ማንኛውንም አስፈላጊ ግብር እና ተጨማሪ እሴት ታክስ እንዲሁም የሊዝ ክፍያ ይከፍላል፡፡
- ተጫራቾች ለጨረታ የቀረበዉን ንብረት ያለበትን ሁኔታ በተመለከተ ከጨረታዉ ቀን በፊት ባሉ የስራ ቀናት እና ሰዓት በባንኩ አበዳሪ ቅርንጫፎች በመቅረብ በሚያዘጋጀዉ ፕሮግራም መሰረት ንብረቱ ያለበትን ሁኔታ መመልከት ይችላሉ፡፡
- ለጨረታው አሸናፊ ባንኩ ባለው የብድር ፖሊሲ መሰረት ብድር ሊያመቻች ይችላል፡፡
- ባንኩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡
ለተጨማሪ መረጃ አዲስ ኢንተርናሽናል ባንክ አ/ማ ሕግ አገልግሎት መምሪያ በስልክ ቁጥር 0115571934 በመደወል መጠየቅ ይቻላል፡፡
አዲስ ኢንተርናሽናል ባንክ አ.ማ