ኦሮሚያ ባንክ በአዋጅ ቁጥር 97/90 (እንደተሻሻለው) በተሰጠው ሥልጣን መሠረት በዋስትና የያዘውን ንብረት ባሉበት በሐራጅ ይሸጣል፡፡
Overview
- Category : Other Foreclosure
- Posted Date : 10/15/2022
- Phone Number : 0115572107
- Source : Reporter
- Closing Date : 11/15/2022
Description
የሐራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ
ኦሮሚያ ባንክ በአዋጅ ቁጥር 97/90 (እንደተሻሻለው) በተሰጠው ሥልጣን መሠረት በዋስትና የያዘውን ንብረት ባሉበት በሐራጅ ይሸጣል፡፡
ተ.ቁ | የተበዳሪው ስም | የንብረት አስያዥ ስም | ለጨረታ የቀረበው መያዣ ንብረት | አበዳሪው ቅርንጫፍ | ንብረቱ የሚገኝበት አድራሻና የቦታ ስፋት | የጨረታ መነሻ/ዋጋ
በብር |
የጨረታዉ ቀንና ሰዓት | ጨረታው የወጣው | ||||
ከተማ | ቀበሌ/ወረዳ | የካርታ ቁጥር | የቦታ ስፋት በካ.ሜ | ቀን | ሰዓት | |||||||
1 | አቶ ታሪኩ ብርቄ ዘውዴ | ተበዳሪው | መኖሪያ ቤት | ሻኪሶ | ሻኪሶ | 04 | EMMLBu/M/Sh 216/06 | 232.4 | 1,666,512.18 | 06/03/2015 | 4፡00-6፡00 | ለመጀመሪያ ጊዜ |
2 | ኑዓሚን ሆቴልና መዝናኛ ኃ/የተ/የግ/ማ | ተበዳሪው | የንግድ ቤት | ጀሞ | አርሲ ነገሌ ወረዳ | ደካ ሆራ ቀዶ | WLBN8636/2007 | 3ሄክታር | 22,892,856.39 | 07/03/2015 | 3:00-5:00 | ለሶስተኛ ጊዜ |
- ተጫራቾች ከጨረታው ቀን በፊት ንብረቶቹ በሚገኙበት አድራሻ ቀርበው ማየት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታውን መነሻ ዋጋ 25% የጨረታ ማስከበሪያ ቦንድ በባንክ ክፍያ ማዘዣ ሲ.ፒ.ኦ አሰርተው ከጨረታው ቀን በፊት ማስያዝ ወይም ጨረታው በሚካሄድበት ዕለት ጨረታው ከመከፈቱ በፊ ይዘው መቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ በጨረታው የተሸነፉ ተጫራቾች ያስያዙት ገንዘብ ይመለስላቸዋል፡፡
- ጨረታው በሰንጠረዡ ላይ በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት ባለዕዳዎቹ ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው፣ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸውና ታዛቢዎች በተገኙበት ተ.ቁ 1 ኦሮሚያ ባንክ ሻኪሶ ቅርንጫፍ ውስጥ ፣ ተ.ቁ 2 በኦሮሚያ ባንክ ዋና መስሪያ ቤት 10ኛ ፎቅ የቦርድ መሰብሰቢያ አዳራሽ ውስጥ ይካሄዳል፡፡
- በሰንጠረዡ ላይ በተጠቀሰው የጨረታ ቀን ባለዕዳዎቹ ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው ባይገኙም ጨረታው ይካሄዳል፡፡
- ጨረታውን ያሸነፈ ተጫራች አሸናፊ መሆኑ በጽሁፍ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ ያሸነፈበትን ዋጋ በ15 ቀን ውስጥ ለባንኩ አጠቃሎ ገቢ ማድረግ ይኖርበታል፡፡
- ከላይ በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ገቢ የማያደርግ ተጫራች ጨረታው ተሰርዞ ያስያዘው ገንዘብም አይመለስለትም፡፡
- በባንኩ ብድር ፖሊሲ መሰረት የሚፈለገውን ማስረጃ አሟልቶ ለቀረበ የጨረታ አሸናፊ ብድርን በተመለከተ ቀርቦ የባንኩን የብድር መምሪያ ማነጋገር ይችላል፡፡
- ንብረቱ በገዢው ስም እንዲዞር ባንኩ ለሚመለከተው መንግስታዊ አካል ደብዳቤ ይጽፋል፡፡
- ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 011 557 2107/011 558 6497 ዋና መ/ቤት ህግ አገልግሎት ዳይሮክቶሬት ወይም ለተ.ቁ. 1 በ 046-334-03 89 ሻኪሶ ቅርንጫፍ ፣ ለተ.ቁ. 2 በ 0114712935/37 ጀሞ ቅርንጫፍ ደውለው መጠየቅ ይቻላል፡፡
- ጨረታው ከመካሄዱ በፊትም ሆነ ከተካሄደ በኃላ ባንኩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ወይም ብድሩ ከተከፈለ ጨረታውን የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ጨረታውን ያሸነፈ ተጫራች ለመንግስት የሚከፈለውን የስም ማዛወሪያ፤ አስፈላጊ ግብር እና ተጨማሪ እሴት ታክስ ይከፍላል፡፡
- የንብረቱ ጨረታ አሸናፊ ውዝፍ የሊዝ ክፍያ ካለ የሚከፍውን ክፍያ ለመክፈል ንብረቱ በሚገኝበት የወረዳ ወይም ከተማ አስተዳደር በመቅረብ የሊዝ ውል መዋዋል አለበት፡፡ ኦሮሚያ ባንክ