የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የጥበቃና ፍተሻ አገልግሎት (Security Services) መስጠት የሚችሉ ህጋዊ ድርጅቶችን አወዳድሮ በግልጽ ጨረታ የጥበቃና ፍተሻ አገልግሎት (Security Services) ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
Overview
- Category : Security & Protection Equipment Guarding
- Posted Date : 10/19/2022
- Phone Number : 0115177006
- Source : Reporter
- Closing Date : 10/24/2022
Description
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ
የግዥ ጨረታ ማስታዎቂያ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የጥበቃና ፍተሻ አገልግሎት (Security Services) መስጠት የሚችሉ ህጋዊ ድርጅቶችን አወዳድሮ በግልጽ ጨረታ የጥበቃና ፍተሻ አገልግሎት (Security Services) ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ በዚሁ መሰረት ለዚሁ ጨረታ የተዘጋጀውን ሰነድ በማይመለስ 100.00 (መቶ ብር ብቻ) በአዲሱ ህንጻ ምድር ቤት በመክፈል የጨረታ ሰነዱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ህንጻ ቁጥር 2፣ 5ተኛ ፎቅ የግዥ አገልግሎት አስተዳደር በመውሰድ መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
- ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ህጋዊነት ማረጋገጫ ሰነድ በማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- የ2014 ዓ.ም ታደሰ የንግድ ሥራ ፈቃድ፤
- የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ የምስክር ወረቀት፤
- የግብር ከፋይ ምዝገባ ሰርተፊኬት፤
- ወቅታዊ ግብር ስለመከፈሉ እና በመንግስት ጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችል ሰርተፍኬት (Tax clearance certificate) ከገቢዎች ባለስልጣን ማቅረብ የሚችል እና
- የምዝገባ የምስክር ወረቀት (የመንግስት መሥሪያ ቤቶች በሚፈጽሙት የዕቃና አገልግሎት ግዥ ለመሳተፍ የተሰጠ የምስክር ወረቀት)፡፡
- ተጫራቾች የጨረታውን ጠቅላላ ዋጋ 2% የጨረታ ማስከበሪያ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፤
- ባንኩ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
የጨረታ መዝጊያ ቀን እና ሰዓት
- ጥቅምት 24 ቀን 2015 ዓ.ም
- ጠዋት 04፡00
የጨረታ መክፈቻ ቀን እና ሰዓት
- ጥቅምት 24 ቀን 2015 ዓ.ም
- ጠዋት 04፡30
ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር 011517-70-06/0115175004/011517-5016 ይደዉሉ፡፡