የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከዚህ በታች በሰንጠረዡ የተገለፁትን እና በዕዳ ማካካሻነት የተረከባቸው የተለያዩ ንብረቶችን በዝግ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
Overview
- Category : Industry & Factory Foreclosure
- Posted Date : 07/17/2022
- Closing Date : 08/16/2022
- Phone Number : 0113852139
- Source : Reporter
Description
የጨረታ ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከዚህ በታች በሰንጠረዡ የተገለፁትን እና በዕዳ ማካካሻነት የተረከባቸው የተለያዩ ንብረቶችን በዝግ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
ተ.ቁ
| ለጨረታ የቀረበው ሕንፃ/ንብረት አገልግሎት | ቤቱ/ንብረቱ የሚገኝበት አድራሻ | የቦታው ስፋት ሜ2 | የካርታ/የባለቤትነት ማረጋገጫ ሠነድ ቁጥር
| የጨረታ መነሻ ዋጋ
| |||
ከተማ | ወረዳ | ቀበሌ | የቤት ቁጥር | |||||
1 | የጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ ህንፃ | ሰበታ | ዲማ | 1 | – | 17 ሄክታር | L/2413/2001 | 657,727,708.05 |
2 | የተለያዩ የጨርቃ ጨርቅ ማሽነሪዎች | ሰበታ | ዲማ | 1 | – | – | – | 129‚856‚283.40 |
ጠቅላላ ድምር | 787,583,991.45 | |||||||
3 | ለፋብሪካ እና ለቢሮ አገልግሎት የሚውል በግንባታ ላይ ያለ ህንፃ | ሰበታ | ሃዋስ | ሃሮ ጂላ ፋልሶ | 33‚430 ሜ.ካ | WLBEN/6844/BL9 | 83,274,097.62 | |
4 | መኖሪያ ቤት | ዋጩ /ም.ሐረርጌ/ | ሀብሮ | 85.5 ካ.ሜ | 140‚356.96 | |||
5 | ንግድ ቤት | ገዋኔ | አፋር | 56.82 ካ.ሜ | 304‚358.66 | |||
6 | ንግድ ቤት | ድሬዳዋ | መልካ ጀብዱ | 4‚800.00 | ||||
7 | ወፍጮ ቤት | ገለምሶ | 34‚500.00 | |||||
8 | መኖሪያ ቤት | መተሀራ | ፈንታሌ | 01 | 0186 | 440 | 18/32/1794 | 406‚503.81 |
9 | መኖሪያ ቤት | ጂቱ | ሀሮ | 01 | 268 ካሬ | 22487 | 48‚306.43 | |
10 | ሱቅ | ቆሬ | ሸሬ | 55 ሜ.ካሬ | 54‚954.41 | |||
11 | መጋዘን | ቆሬ | ሸሬ | 57.6 ሜ.ካሬ | 57‚552.25 | |||
12 | መኖሪያ ቤት | ቆሬ | ጎቤ | 90 ሜ.ካሬ | 89‚505.68 | |||
13 | የተለያዩ የስካኒያ ተሽከርካሪ መለዋወጫዎች | አዲስ አበባ | 281‚711.82 | |||||
14 | የትምህርት ቤት ህንፃ | መተማ ዮሐንስ | 03/01 | 4500 ሜ.ካሬ | ኢን-011 | 6‚900‚000.00 |
ማሳሰቢያ
- የንብረቶቹን አጠቃላይ ሁኔታ በግንባር ማየት ለሚፈልጉ ተጫራቾች ባንኩ የጉብኝት ፕሮግራም እንደ አስፈላጊነቱ ሊያዘጋጅ ይችላል፡፡
- በተራ ቁጥር አንድ ላይ ያለው ህንፃ የኦሮሚያ ኢንቨስትመንት ቦርድ ኦገስት 2009 ባሳለፈው ውሳኔ ድርጅቱ እ.ኤ.አ. ከ ኦገስት 25 ቀን 2009 እስከ ፌብርዋሪ 24 ቀን 2089 ድረስ ለ80 ዓመት ይዞታውን ከሊዝ ነጻ በሆነ ክፍያ እንዲገለገሉበት ውል ፈጽሟል፡፡
- በተራ ቁጥር ሦስት ላይ የተገለፀው ፋብሪካ በኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የመሬትና የአካባቢ ጥበቃ ቢሮን ለማቋቋም በወጣው አዋጅ ቁጥር 147/2001 መሰረት ከ30/08/2007 ዓ.ም ጀምሮ ለ45 ዓመት በገጠር መሬት ኪራይ እንዲገለገልበት የምስክር ወረቀት ተሰጥቶታል፡፡
- የሳይገን ዲማ ፋብሪካን አጠቃላይ ሁኔታን የሚያሳይ የቪዲዮ ምስል ባንኩ በዕዳ ማካካሻነት የተረከባቸው ንብረቶች አስተዳደር ክፍል ከሳር ቤት ወደ ቄራ በሚወስደው ዋና መንገድ ከሳልቫቶሪ ዲቬታ የእንጨትና ብረታ ብረት ስራ ጀርባ 50 ሜትር ገባ ብሎ በሚገኘው ወልደማርያም ህንፃ መዳረሻ ፎቅ የቢሮ ቁጥር 011 ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን አንስቶ በአካል በመቅረብ መመልከት ይቻላል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 100.00 /አንድ መቶ/ በመክፈል ከሐምሌ 8 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቄራ ቅርንጫፍ፣ ነቀምት ዲስትሪክት፣ ሻሸመኔ ዲስትሪክት፣ ድሬዳዋ አብይ ቅርንጫፍ ፣ አዳማ ዲስትሪክት እንዲሁም ጎንደር ዲስትሪክት መግዛት ይችላሉ፡፡
- ማንኛውም ተጫራች ሌሎች ተጫራቾች በሰጡት ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ መስጠት አይችልም፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ መነሻ ዋጋውን 25% /ሃያ አምስት በመቶ / የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በባንክ ክፍያ ማዘዣ /CPO/ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ስም በማሰራት ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- በጨረታው አሸናፊ ሆኖ ለሚቀርብ ተጫራች ባንኩ ባለው የብድር ፖሊሲና መመሪያ መሠረት ከፊል ብድር ሊሰጥ ይችላል፡፡
- ለጨረታ ከቀረቡት ንብረቶች መካከል የጨርቃ ጨርቅ ማሽነሪዎቹ ከፋብሪካው ተነጥለው አይሸጡም፡፡
- በተራ ቁጥር 4፣ 8 ፣ 9 እና 12 ላይ ከተጠቀሱት መኖሪያ ቤቶች በስተቀር በሌሎቹ ንብረቶች ላይ በሽያጭ ገንዘብ ላይ የሚታሰብ 15% የተጨማሪ እሴት ታክስ /VAT/ ገዢ ጨምሮ ይከፍላል፡፡
- ተጫራቾች ለንብረቶቹ የሚሰጡትን ዋጋ ከጨረታ ሰነዱ ጋር በተያያዘው የዋጋ ማቅረቢያ ቅጽ ላይ ካሰፈሩ በኋላ የጨረታ ማስከበሪያና ሌሎች አስፈላጊ ሰነዶችን በፖስታ በማሸግ ነሐሴ 09 ቀን 2014 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 እስከ ቀኑ 10፡00 ድረስ
- ከተራ.ቁ 1 ፣ 2 ፣ 3 እና 13 ላይ ያሉ ንብረቶች ከሳር ቤት ወደ ቄራ በሚወስደው ዋና መንገድ ከሳልቫቶሪ ዲቬታ የእንጨትና ብረታ ብረት ስራ ጀርባ 50 ሜትር ገባ ብሎ በሚገኘው ወልደማርያም ህንፃ ምድር ቤት የቢሮ ቁጥር 004
- ከተራ.ቁ 4 እስከ 7 ላይ ለተጠቀሱት ንብረቶች በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ድሬዳዋ ዲስትሪክት ጽ/ቤት
- ተራ.ቁ 8 በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አዳማ ዲስትሪክት ጽ/ቤት
- ተራ ቁጥር 9 በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ነቀምት ዲስትሪክት ጽ/ቤት
- ከተራ.ቁ 10 እስከ ተራ.ቁ 12 ላይ ለተጠቀሱት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሻሸመኔ ዲስትሪክት ጽ/ቤት
- ተራ.ቁ 14 ላይ ለተጠቀሰው በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጎንደር ዲስትሪክት ጽ/ቤት በመቅረብ ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ አስመዝግበው ማስገባት ይኖርባቸዋል፡
- ጨረታው ነሐሴ 10 ቀን 2014 ዓ.ም ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ከላይ በተራ ቁጥር አስራ አንድ ላይ በተገለፁት አድራሻዎች ይከፈታል፡፡
- ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0113-85-21-39 ወይም 0911 48-29-14 አዲስ አበባ፣ 0912-32-08-54 ድሬደዋ ፣ 0221-11-22-75 እና 0221-11-27-50 አዳማ ፣ 057-661-76-73 እና 057-771-09-35 ነቀምት ዲስትሪክት ፣ 046-110-42-72 ሻሸመኔ ዲስትሪክት እና 0581-26-00-47 ጎንደር ዲስትሪክት በመደወል ወይም ከላይ በተጠቀሰው አድራሻ ባንኩ በዕዳ ማካካሻነት የተረከባቸው ንብረቶች አስተዳደር ክፍል በግንባር ቀርቦ መጠየቅ ይቻላል፡፡
- ባንኩ የተሻለ መንገድ ካገኘ በማንኛውም ጊዜ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው ፡፡