ፀሐይ ኢንዱስትሪ አ.ማ ቃሊቲ ብረታ ብረት ፋብሪካ በዋናው መ/ቤት ለሚያሰራው የመጋዘን ቁጥር 2 ግንባታ ስራ ደረጃ 5 እና ከዚያ በላይ የሆኑ የሕንፃ ስራ ተቋራጮችን በጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል፡፡

Overview

  • Category : Construction Service & Maintenance
  • Posted Date : 06/05/2021
  • Closing Date : 07/06/2021
  • Phone Number : 0114340110
  • Source : Reporter

Description

የመጋዘን ግንባታ የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 013/2013

ፀሐይ ኢንዱስትሪ አ.ማ ቃሊቲ ብረታ ብረት ፋብሪካ በዋናው መ/ቤት ለሚያሰራው የመጋዘን ቁጥር 2 ግንባታ ስራ ደረጃ 5 እና ከዚያ በላይ የሆኑ የሕንፃ ስራ ተቋራጮችን በጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል፡፡

ስለሆነም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ የስራ ተቋራጮች በጨረታው እንድትሳተፉ ይጋብዛል፡፡

  1. የግንባታ ስራ ፍቃድ ደረጃቸው 5 እና ከዚያ በላይ የሆኑ፡፡
  2. ተጫራቾች በመስኩ የታደሰ እና ሕጋዊ የንግድ ስራ ፈቃድ ያላቸው፣ በሚመለከተው መ/ቤት የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው፡፡
  3. ተጫራቾች ለዚሁ የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ቃሊቲ መናኸሪያ አካባቢ ፣ ከቶታል ነዳጅ ማደያ ፊት ለፊት፣ ከካፍደም ሲኒማ በኩል 700 ሜትር ገባ ብሎ በሚገኘው ከፋብሪካው የግዥ ዋና ክፍል የማይመለስ ብር 200 በመክፈል መውሰድ ይችላሉ፡፡
  4. የጨረታው ተሳታፊዎች የሚያቀርቡት ጨረታ ሰነድ ፋይናንሺያል እና ቴክኒካል በሚል ተለይቶ ለየብቻው አንድ ኦርጅናል እና አንድ ኮፒ በታሸገ ፖስታ በማድረግ በፋብሪካው ግዢ ዋና ክፍል ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  5. ጨረታው ሰኔ 29 ቀን 2013 ዓ.ም 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በእለቱ ተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
  6. ፋብሪካው የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ፀሐይ ኢንዱስትሪ አ.ማ

ቃሊቲ ብረታ ብረት ፋብሪካ

ዋና መ/ቤት ስልክ 011-4-34-01-10/011-4-34-40-06