ጀስቲስ ህንፃ ስራ ተቋራጭ ኃ.የተ.የግ.ማህበር ያገለገሉ የኮንስትራክሽን ማሽነሪዎችን እና የኮንስትራክሽን እቃዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
Overview
- Category : Other Sale
- Posted Date : 10/29/2021
- Phone Number : 0911224409
- Source : Reporter
- Closing Date : 11/20/2021
Description
የተሸከርካሪዎች እና የኮንስትራክሽን ማሽነሪዎች ሽያጭ ጨረታ ማስታወቂያ
ድርጅታችን ጀስቲስ ህንፃ ስራ ተቋራጭ ኃ.የተ.የግ.ማህበር ያገለገሉ የኮንስትራክሽን ማሽነሪዎችን እና የኮንስትራክሽን እቃዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም ለመግዛት የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች ለዚሁ ተብሎ የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ በቅድሚያ የማይመለስ ብር 100 (አንድ መቶ ብር) ከፍሎ በመግዛት ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ላይ ከወጣበት እለት ጀምሮ ለሃያ ተከታታይ ቀናት የሚሸጡትን ማሽነሪዎችንና የኮንስትራክሽን እቃዎች ከአሽዋ ሜዳ ወደ ታጠቅ በሚወስደው ታጠቅ ኢንደስትሪ መንደር ከሜቴክ አለፍ ብሎ በስተቀኝ በኩል ታጥፈው በመግባት ከዚያም ከፊርደውስ ማርብል በስተቀኝ በኩል ትንሽ አለፍ ብሎ ከድርጅቱ እህት ኩባንያ ከሆነው አኪዩሬት ኮንክሪት አቅራቢዎች ኃ/የተ/የግ/ማህበር አጥር ግቢ ውስጥ ሄዶ ማየት የሚችሉ ሲሆን የጨረታ ሰነዱን ለመግዛት ለገሀር ኮሜርስ ኮሌጅ ጀርባ ከሚገኘው መዚድ ህንፃ 6ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 612 በመግዛት እቃውን የሚገዙበትን ዋጋ በጨረታ ሰነዱ ላይ በመሙላት በፖስት አሽጎ ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 20ኛው ቀን ጠዋት 4፡30 ሰዓት ድረስ የጨረታ ሰነዱን የገዙበት ቢሮ ማስገባት የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን፣ ጨረታው በዚሁ እለት ከጠዋቱ 5፡00 ላይ ተጫራቾች ወይም ህገዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የሚከፈት መሆኑን እንገልፃለን፡፡
- ማሳሰቢያ ድርጅቱ የተሸለ አማራጭ ካገኘ ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ በሰልክ ቁጥር 09-11-22-44-09/09-41-96-96-96