የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት በአዲስ አበባ ቅርንጫፎቹ ያከማቸውን የተለያዩ ሸቀጦች ወደ ተለያዩ የክልል ቅርንጫፎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማጓጓዝ ይፈልጋል፡፡
Overview
- Category : Transport Service
- Posted Date : 02/16/2022
- Phone Number : 0113692647
- Source : Reporter
- Closing Date : 02/22/2022
Description
የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት
የሸቀጥ ማጓጓዥ የጭነት አገልግሎት ግዥ ጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር 016/14
ድርጅታችን በአዲስ አበባ ቅርንጫፎቹ ያከማቸውን የተለያዩ ሸቀጦች ወደ ተለያዩ የክልል ቅርንጫፎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማጓጓዝ ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም በጨረታው መካፈል የሚፈልጉ ድርጅቶች፡-
- በዘርፉ የታደሰ ንግድ ሥራ ፍቃድ፣ የብቃት ማረጋገጫ፣ ተጨማሪ እሴት ታክስና የግብር ከፋይነት ምዝገባ ሠርተፍኬት ያላቸው መሆን ይገባቸዋል፡፡
- በጨረታ መመሪያው ላይ የተቀመጡትን ግዴታዎች በሙሉ መወጣት የሚችሉ መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ለጨረታው የተዘጋጀውን ዝርዝር የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል ፒያሳ በተለምዶ አትክልት ተራ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ከሚገኘው የድርጅቱ ዋና መስርያ ቤት የኢንዱስትሪ ውጤቶች ግዥ ዳይሬክቶሬት በመቅረብ መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ የሚሆን ብር 100,000 (አንድ መቶ ሺ ብር) በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ማዘዣ (ሲ.ፒ.ኦ) ብቻ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- የጨረታ መወዳደሪያ ዋጋቸውን ከላይ ከተጠቀሱት ህጋዊ ሠነዶች ጋር በታሸገ ኤንቨሎፕ አንድ ኦሪጅናል እንዲሁም አንድ ኮፒ በማድረግ እስከ የካቲት 15 ቀን 2014 ዓ.ም እስከ 8፡00 ሰዓት ድረስ ማቅረብ ይችላሉ፡፡
- ጨረታው በተመሳሳይ የካቲት 15 ቀን 2014 ዓ.ም ከሰዓቱ 8፡10 ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0113-69-26-47/0113-69-24-39
www.eiide@eiide.com.et