አዲስ ኢንተርናሽናል ባንክ አ.ማ ለሰጠዉ ብድር በዋስትና የያዛቸዉን ንብረቶች በአዋጅ ቁጥር 97/1990 በተሰጠዉ ስልጣን መሰረት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡

Addis-International-Bank-logo-reportertenders

Overview

  • Category : House & Building Foreclosure
  • Phone Number : 0115571934
  • Source : Reporter
  • Posted Date : 05/04/2022
  • Closing Date : 06/04/2022

Description

ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ የሐራጅ ማስታወቂያ

አዲስ ኢንተርናሽናል ባንክ አ.ማ ለሰጠዉ ብድር በዋስትና የያዛቸዉን ንብረቶች በአዋጅ ቁጥር 97/1990 በተሰጠዉ ስልጣን መሰረት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡በዚሁ መሰረት ማንኛዉም ተጫራች ሐራጁ በሚካሄድበት ቀን ንብረቶቹ በሚገኙበት ቦታ በመገኘት በጨረታዉ ተወዳድሮ ንብረቶቹን እንዲገዛ ተጋብዟል፡፡

ተ.ቁየተበዳሪዉ ስምየንብረት አስያዥ ስምለጨረታ የቀረበዉ የመያዣ ንብረት አይነትንብረቱ የሚገኝበት አድራሻየባለቤትነት ማረጋገጫ ቁጥርየቦታዉ ስፋት በካሬ ሜትርየጨረታዉ መነሻ ዋጋጨረታዉ የሚከናወንበት ቦታጨረታዉ የሚከናወንበት ቀንና ሰዓት
ከተማክ/ከተማና ወረዳ
1ኤ እና ኤ ኢምፖርት እና ኮሚሽን ኤጀንት ኃ/የተ/የግ/ማህበርወ/ሮ አዘነች ይንበርበሩመኖሪያ ቤትአዲስ አበባኮ/ቀ/ክ/ከተማ ወረዳ 04ኮ/ቀ/ማ/ን/መ/34/3652/00 158 ካ.ሜ2,189,411.36ንብረቱ የሚገኝበትግንቦት 27 ቀን 2014 ዓ/ም ከጠዋቱ 4.00-6.00 ሰዓት
2ኤ እና ኤ ኢምፖርት እና ኮሚሽን ኤጀንት ኃ/የተ/የግ/ማህበርአቶ አሰፋ ተድላመኖሪያ ቤትአዲስ አበባአቃቂ ቃሊቲ

ወረዳ 08

00390/1419 ካ.ሜ3,135,740.88ንብረቱ የሚገኝበትግንቦት 29 ቀን 2014 ዓ/ም ከጠዋቱ 4.00-6.00 ሰዓት
3ደዴፎ ጤኔሾ ቦቶኒደዴፎ ጤኔሾ ቦቶኒመኖሪያ ቤትአዳማቀበሌ 02347Q/3876/98200 ካ.ሜ1,180,681.19ንብረቱ የሚገኝበትግንቦት 30 ቀን 2014 ዓ/ም

ከጠዋቱ 4.00-6.00 ሰዓት

  • ተጫራቾች የጨረታዉን መነሻ ዋጋ 25% በባንኩ የክፍያ ማዘዣ ሰነድ(cpo) አሰርቶ በጨረታው እለት በመቅረብ መጫረት ይችላሉ፡፡
  • ጨረታዉ በማስታወቂያዉ ላይ በተጠቀሰዉ ቀንና ሰዓት ባለዕዳዎቹ ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸዉ፣ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸዉ፣ታዛቢዎች በተገኙበት፣የመያዣ ንብረቱ በሚገኝበት ክ/ከተማ የሚካሄድ ይሆናል፡፡ ጨረታው ባለእዳዎቹ እና አስያዦቹ በእለቱ ባይገኙም የሚከናወን ይሆናል፡፡
  • የጨረታዉ አሸናፊ ያሸነፈበትን ዋጋ ጨረታዉ ከተከናወነበት ማግስት ጀምሮ በሚቆጠር 15 ቀን ዉስጥ ለባንኩ ገቢ ማድረግ ይኖርበታል፡፡ በእነዚህ ቀናት ዉስጥ ካልከፈለ ግን ለጨረታ ያስያዘዉ ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ሆኖ ጨረታዉ ተሰርዞ ለሐራጅ የሚቀርብ ይሆናል፡፡በጨረታዉ ተሳትፈዉ ላላሸነፉት ተጫራቾች ያስያዙት ጥሬ ገንዘብ ወይም ሲፒኦ ወዲያኑ ተመላሽ ይደረግላቸዋል፡፡
  • ኃ/የተ/የግል ማህበርን ወይም አክሲዮን ማህበርን ወክሎ መጫረት የሚፈልግ ሥራ አስኪያጅ ወይም ም/ሥራ አስኪያጅ የድርጅት የመመስረቻ ጽሑፍ ይዞ መቅረብ ያለበት ሲሆን የሥራ አስኪያጅ ወይም የም/ሥራ አስኪያጅ ለዉጥ ተደርጎ ከሆነ ይሀንኑ የሚገልጽ በሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ጽ/ቤት የቃለ ጉባኤ ከመመስረቻ ጽሑፍ እና መተዳደሪያ ደንብ ጋር ይዞ መቅረብ አለበት፡፡
  • የጨረታዉ አሸናፊ ለመንግስት የሚከፈለዉን አስፈላጊ ግብር እና ማንኛውንም ክፍያ እና ተጨማሪ እሴት ታክስ እንዲሁም የሊዝ ክፍያ ይከፍላል፡፡
  • ተጫራቾች ለጨረታ የቀረበዉ ንብረት ያለበትን ሁኔታ በተመለከተ ከጨረታዉ ቀን በፊት ባሉ የስራ ቀናት እና ሰዓት በባንኩ ቅርንጫፎች በመቅረብ በሚያዘጋጀዉ ፕሮግራም መሰረት ንብረቱ ያለበትን ሁኔታ መመልከት ይችላለ፡፡
  • ለተጨማሪ መረጃ አዲስ እንተርናሽናል ባንክ አ/ማ ሕግ አገልግሎት በስልክ ቁጥር 0115571934፣ መካኒሳ ቅርንጫፍ [email protected] አዳማ ቅርጫፍ 022 2119050 በመደወል መጠየቅ ይቻላል፡፡
  • ባንኩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡

አዲስ ኢንተርናሽናል ባንክ አ.ማ.