ፀሐይ ባንክ አ.ማ ከዚህ በታች በተገለጹት የሥራ መደቦች የሰው ኃይል በማቅረብ ሙያዊ ፍቃድ ያላቸው ድርጅቶችን በማወዳደር አገልግሎት መግዛት ይፈልጋል፡፡
Overview
- Category : Purchases
- Posted Date : 05/09/2022
- Phone Number : 0114705055
- Source : Reporter
- Closing Date : 05/31/2022
Description
የሰው ኃይል አቅርቦት የአገልግሎት ግዥ
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር ፀባ/006/2014
ባንካችን ከዚህ በታች በተገለጹት የሥራ መደቦች የሰው ኃይል በማቅረብ ሙያዊ ፍቃድ ያላቸው ድርጅቶችን በማወዳደር አገልግሎት መግዛት ይፈልጋል፡፡
ተ.ቁ | የሥራው/የአገልግሎቱ ዓይነት |
1 | ጥበቃ |
2 | የገንዘብ አጃቢ (ጥበቃ) |
3 | መልዕክት ሰራተኛ |
4 | ጽዳት /ከነጽዳት ዕቃዎች አቅርቦት ጋር/ |
5 | ጽዳትና መልዕክት ሰራተኛ |
6 | ሾፌር(የመኪና አሽከርካሪ) |
7 | ሾፌር መካኒክ (የመኪና) |
8 | ሞተረኛ |
9 | መኪና አጣቢ |
10 | የጉልበት ሰራተኛ |
ስለሆነም በጨረታው የሚወዳደሩ ድርጅቶች የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል፤
- ከሠራተኛና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ለ2014 ዓ.ም የታደሰ የቅጥር ሥራ ፈቃድ ማቅረብ አለባቸው ፡፡
- ተጫራቾች ከጨረታ ሰነዶቹ ጋር የታደሰ የንግድ ፈቃድ ቅጅ ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ የምስክር ወረቀት፣ የቲን የምስክር ወረቀት እና ከገቢዎች ሚኒስቴር ከግብር ነፃ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ከግንቦት 02 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት የሥራ ቀኖች ማለትም ከሰኞ እስከ አርብ ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት እስከ 6:00 ሰዓት እና ከሰዓት በኋላ ከ7:00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 11:00 ሰዓት እንዲሁም ቅዳሜ ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት እስከ 6:00 ሰዓት የማይመለስ መቶ ብር /100.00/ በመክፈል መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን የጨረታ ሰነድ በሰም በታሸገ ፖስታ እስከ ግንቦት 23 ቀን 2014 ዓ.ም ከቀኑ 9፡00 ሰዓት ድረስ በዋና መ/ቤት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ ጨረታው በዚሁ ዕለት በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከቀኑ 9፡30 ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በባንኩ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ሰነድ /Bid Bond/ ብር 25‚000.00 ቢያንስ ለ90 ቀናት ጸንቶ የሚቆይ በባንክ በተመሰከረለት የባንክ ዋስትና ወይም ሲፒኦ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡ የጨረታው መዝጊያ ሰዓት ካለፈ በኋላ የሚመጣ ማንኛውም የጨረታ ሰነድ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡
- ተጫራቾች በሥራው/ዘርፉ/ ለ3 ዓመታትና ከዚያ በላይ የቆዩ መሆን አለባቸው፤ ከሶስት ዓመት በታች ልምድ ያለው ድርጅት ተቀባይነት አይኖረውም፡፡
- ባንኩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለተጨማሪ መረጃ፤
- በስልክ ቁጥር +251 11 4 70 50 55 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡ በአካል በመቅረብ መረጃ ማግኘት ለሚፈልጉ ተጫራቾች ግሎባል ሆቴል ፊት ለፊት ፣ ባላገሩ ህንፃ 5ኛ ፎቅ የባንኩ ፋሲሊቲስ ማኔጅመንት መምሪያ ማግኘት ይችላሉ፡፡
ፀሐይ ባንክ አ.ማ
ስልክ +251 11 4 70 50 55/+251 11 4 70 56 13
አዲስ አበባ, ኢትዮጵያ