ሕብረት ባንክ አ.ማ. በአለም ገና ቅርንጫፉ በኩል ለሰጠዉ ብድር በመያዣነት የያዛቸዉን ከዚህ በታች የተመለከቱትን የባንክ አክሲዮኖች በአዋጅ ቁጥር 97/90 እና 216/1992 በተሰጠዉ ስልጣን መሰረት በግልጽ ሐራጅ (ጨረታ) አወዳድሮ ይሸጣል፡፡

hibret-bank-done-logo-reportertenders-6

Overview

  • Category : Other Foreclosure
  • Posted Date : 05/14/2022
  • Closing Date : 05/31/2022
  • Phone Number : 0113662022
  • Source : Reporter

Description

ለሁለተኛ ጊዜ የወጣ የሐራጅ ማስታወቂያ፤

ሕብረት ባንክ አ.ማ. በአለም ገና ቅርንጫፉ በኩል ለሰጠዉ ብድር በመያዣነት የያዛቸዉን ከዚህ በታች የተመለከቱትን የባንክ አክሲዮኖች በአዋጅ ቁጥር 97/90 እና 216/1992 በተሰጠዉ ስልጣን መሰረት በግልጽ ሐራጅ (ጨረታ) አወዳድሮ ይሸጣል፡፡

የቅርንጫፍ ስምየተበዳሪ ስምየንብረት አስያዦች ስምአክሲዮኖቹ የሚገኙበት ድርጅት (አ.ማ.)የሰርተፊኬት ቁጥርየአክሲዮን ብዛትየአንዱ አክሲዮን ዋጋ /በብር/የሐራጅ መነሻ ዋጋ

/በብር/

ሐራጁ የሚካሄድበት ቀንና ሰዓት
አለም ገናአቶ ቢኒያም በየነ አብርሃአቶ ቢኒያም በየነ አብርሃአንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ አ.ማAAG 07188116,59425 (ሃያ አምስት) ብር25 (ሃያ አምስት) ብርግንቦት 23      ቀን 2014 ዓ.ም ከጠዋቱ ከ4፡00 እስከ 6፡00 ሰዓት
AAI 0718820,00025 (ሃያ አምስት) ብር25 (ሃያ አምስት) ብር

    የሐራጅ ደንቦች

  1. ተጫራቾች መጫረት የሚፈልጉትን የአክሲዮን ብዛት በ100 (አንድ መቶ) አባዝተው የሚገኘው መጠን ላይ አንድ አራተኛ በባንክ ክፍያ ማዘዣ (ሲ.ፒ.ኦ.) ብቻ በማስያዝ መጫረት ይችላሉ፡፡
  2. አሸናፊ የሆነዉ ተጫራች ያሸነፈበትን ቀሪ ገንዘብ በአስራ አምስት (15) ቀናት ዉስጥ አጠቃልሎ ካልከፈለ ያስያዘዉ ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ሆኖ ሐራጁ ይሰረዛል፡፡ በተጨማሪም ንብረቱ ድጋሚ ለሀራጅ ሲቀርብ ለሚታየዉ የዋጋ ልዩነት ይጠየቃል፡፡
  3. በሐራጅ ላይ መገኘት የሚችሉት ተጫራቾች፣ ተበዳሪዎች እና አስያዦች ብቻ ናቸዉ፡፡
  4. የሐራጅ ሽያጩ የሚካሄደዉ አዲስ አበባ ንግድ ሥራ ኮሌጅ ፊትለፊት በሚገኘው የባንኩ አዲሱ ዋና መሥሪያ ቤት፣ 26ኛ ፎቅ ባለዉ የሕግ መምሪያ አዳራሽ ዉስጥ ነዉ፡፡
  5. የተጫራቾች ምዝገባ ከሐራጁ መዝጊያ ሰዓት ሰላሳ ደቂቃ በፊት ይጠናቀቃል፡፡ በሐራጁ ሰላሳ (30) ደቂቃዎች የተጫራች ምዝገባ አይካሄድም፡፡
  6. የተጨማሪ እሴት ታክስ እና ሌሎች ገዥ እንዲከፍላቸዉ በህግ የተወሰኑ የታክስና ግብር የስም ማዛወሪያ ጭምር /የጨረታዉ አሸናፊ/ገዥዉ ይከፍላል፡፡
  7. ባንኩ ጨረታዉን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡
  8. በጨረታው ለመሳተፍ የሚቀርቡ ተጫራቾች ኢትዮጵያዊ ወይም ትውልደ ኢትዮጵያዊ ለመሆናቸዉ ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው፡፡
  9. አንድ ተጫራች ከላይ በሰንጠረዡ የተገለጸው የአክሲዮን ብዛት በሙሉም ሆነ በከፊል ለመግዛት መጫረት ይችላል፡፡
  • የጨረታው አሸናፊ የሚሆነው ለአንድ አክሲዮን በሚቀርበው ከፍተኛ ዋጋ መሰረት ከከፍተኛው ወደ ዝቅተኛ በቀረበው ዋጋ ቅደም ተከተል ነው፡፡
  • አግባብነት ያላቸው በኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ የወጡ መመሪያዎች ሁሉ ተፈጻሚ ይሆናሉ፡፡
  • ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0113662022 አለም ገና ቅርንጫፍ ወይም 0114-70 03 15/69/47 ሕግ አገልግሎት መምሪያ ደዉለዉ መጠየቅ ይችላሉ፡፡