ዳሸን ባንክ ከኢትዮጵያ ውጭ ለንግድ ሥራ የሚጓዙ ደንበኞቹ ግብይታቸውን በውጭ ምንዛሪ ለመፈጸም የሚያስችላቸው የዴቢት ካርድ ይፋ ሲያደርግ፣ አቢሲኒያ ባንክ ደግሞ ዓይነ ሥውራን የሚገለገሉበት ኤቲኤም አገልግሎት ላይ አዋለ፡፡ ሁለቱ ባንኮች ሐሙስ ጥቅምት 25 ቀን 2014 ዓ.ም. ይፋ ያደረጉዋቸው አዲሶቹ አገልግሎቶቻቸው በባንክ ኢንዱስትሪው ውስጥ ለመጀመርያ ጊዜ የሚተገበሩ ስለመሆናቸው ባንኮቹ በሰጡዋቸው መግለጫዎች አመልክተዋል፡፡ ዳሸን ባንክ አሜሪካን ኤክስፕሬስ የተሰኘውን …
መርካቶዎች እየተፈተኑባቸው ያሉ ችግሮች
ከሁለት አሠርት በላይ በንግድ ላይ ለተሰማራው አቶ ቴድሮስ ፍቅሩ፣ መርካቶ ማለት ከሰፈርም ከመነገጃነትም በላይ ነው። ‹‹ተወልጄ አድጌ ሀብት ያፈራሁባት ልዩ ሥፍራ ናት›› በማለት መርካቶን ያወድሳል የ43 ዓመቱ ጎልማሳ አቶ ቴድሮስ። በልብስ ምርቶች ንግድ፣ በቤትና ቢሮ ዕቃዎች ማምረትና መሸጥ ላይ የተሰማራው አቶ ቴድሮስ፣ በመርካቶ ሕይወቱን ከልጅነት እስከ አዋቂነት ቢያሳልፍም በመዲናዋ ነግዶ ሀብት ማፍራት ቀላል እንዳልሆነ ያነሳል። ‹‹ምንም እንኳን መርካቶ ለመላው ኢትዮጵያውያን ምርት የሚከፋፈልባትና የሚቀርብባት የሁላችንም የገበያ መዲና ብትሆንም፣ ከቀን ወደ ቀን ሠርቶ መለወጥ እየከበደ ነው›› የሚለው አቶ ቴድሮስ፣ ለዚህም መንግሥትና ሕገወጥ ነጋዴዎችን ይወቅሳል። ከ30 ሺሕ በላይ ሱቆችና ከ700 ሺሕ በላይ ሸማቾች፣ ነጋዴዎችና የንግድ ሠራተኞች በየቀኑ ገብተው ይወጡባታል ተብሎ በምትታመነው መርካቶ፣ የተለያዩ ችግሮችን መመልከት አዲስ ነገር አይደለም። ከሌባና ቀማኞች ገንዘብና ንብረታቸውን ለመጠበቅ ከሚሞክሩ ሸማቾች እስከ በሙስና የተዘፈቁ አንዳንድ የገቢዎች ሠራተኞች ለመሰወር የሚሞክሩ ሠራተኞችን ማየት የተለመደ ጉዳይ ነው። ሁሉም ዓይነት ነጋዴዎች በየፊናቸው እንደ ዘርፋቸው ሁኔታ የተለያዩ ተግዳሮቶች ቢገጥማቸውም ሪፖርተር በመርካቶ በመገኘት ባደረገው ዳሰሳ በአብዛኛው የሚያነሱት ቅሬታዎች ፍትሐዊ የንግድ ሥርዓት አለመኖር፣ ለሙስና በር የከፈተ የተጨማሪ እሴት ታክስ አተገባበርንና የመሠረተ ልማቶች አለሟሟላትን ነው። ‹‹የፍትሐዊንግድያለ›› የፌዴራልም ሆነ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እንዲሁም የወረዳ ንግድ ቢሮዎች የተገልጋዮች ቻርተር ላይ በጉልህ ከተቀመጡ ጉዳዮች አንዱ ፍትሐዊ፣ ግልፅና በውድድር ላይ የተመሠረተ የንግድ ሥርዓትን ማስፈን ነው። ይህንንም መተግበር ከመንግሥት አጀንዳዎች መካከል መሆኑን የመንግሥት ባለሥልጣናት በተደጋጋሚ ያነሳሉ። ይሁን እንጂ የተጻፈው አልያም የተወራው ከትግበራው አኳያ ፈፅሞ የተለየ መሆኑን ነጋዴዎች ይናገራሉ። በመርካቶ አመዴ ተራ በጫማ ችርቻሮ ንግድ ላይ የተሰማሩት አቶ አማኑኤል መንግሥቱ እንደሚናገሩት፣ የንግድ ሥርዓቱ ላይ የፍትሐዊነት ችግሮች መታየት ከጀመሩ ሰንበትበት ብለዋል። የመንገድ ላይ ንግድ መስፋፋትን እንደ ማሳያ የሚያነሱት አቶ …
የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው የተጋረጠበት አደጋ
የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ችግር ውስጥ መሆኑ መነገር ከጀመረ ሰነባብቷል፡፡ በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየታየ ያለው የኮንስትራክሽን ግብዓት ዕቃዎች ዋጋ ከሚገባው በላይ መሰቀል፣ የግንባታውን ዘርፍ በእጅጉ እየጎዳ ነው፡፡ ሰሞኑን የኢትዮጵያ ኮንትራክተሮች ማኅበር እንዳመለከተውም፣ አሁን በኮንስትራክሽን ዘርፍ ውስጥ እየታየ ያለው ችግር አጠቃላይ በግንባታ ሥራዎች ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ከመፍጠሩም በላይ፣ አፋጣኝ መፍትሔ ካላገኘ የበርካታ ፕሮጀክቶች ሥራ ሊቆም እንደሚችል ነው፡፡ …